ናምሩድ
From Wikipedia, the free encyclopedia
በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲሁም በአፈ ታሪክ፣ ናምሩድ (ዕብራይስጥ נִמְרוֹד /ኒምሮድ/) የኩሽ ልጅ፣ የካም ልጅ ልጅ እና የኖህ ልጅ-ልጅ-ልጅ ሲሆን የሰናዖር ንጉሥና 'በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ' ይባላል። በመጽሐፍ ቅዱስ ስሙ የሚገኘው በኦሪት ዘፍጥረት 10፣ በዜና መዋዕልና በትንቢተ ሚክያስ ብቻ ነው። እነዚህ መጻሕፍት ስለ ናምሩድ ብዙ ባይነገሩንም፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ስለሱ ያሉት ትውፊቶች ግን በርካታ ናቸው። ከነዚህም ትውፊቶች መካከል ከሁሉ የታወቀው የባቢሎን ግንብ እንዲገነባ ያዘዘ መሆኑ ነው።