እቴጌ ምንትዋብ
From Wikipedia, the free encyclopedia
እቴጌ ምንትዋብ በዙፋን ስሟ ብርሃን ሞገስ በ1698 ዓ.ም. ከአባቷ ደጅአዝማች መንበር እና እናቷ ልዕልት እንኮይ በቋራ፣ ጎንደር ስትወለድ የክርስትና ስሟ ወለተ ጊዮርጊስ ነበር። እናቷ ልዕልት እንኮይ ከዓፄ ሚናስ ዘር የምትወለድ እንደነበረች ይጠቀሳል[1]። ምንትዋብ በ18ኛው ክፍልዘመን ኢትዮጵያ ላይ ብዙ አሻራ ትታ የለፈች ንቁ፣ ሃይለኛና ተራማጅ መሪ ነበረች። ከባሏ ዓፄ በካፋ ዘመን ጀምሮ እስከ ልጇ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ እና ልጅ ልጇ ዓፄ እዮዋስ ዘመን ድረስ ለ40 አመታት የአገሪቱ እኩል መሪ የነበረች ናት። በዚህች መሪ ዘመን በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ የህንጻዎች ግንባታና የቤተክርስቲያን ድረሰት፣ እንዲሁም ስነ ጥበብ እድገት ታይቷል። በፋሲል ግቢ የመጨረሻውን ግንብ ያስገነባችው ምንትዋብ ነበረች። ከልጆቿ የእድሜ አናሳነትና እራሷም በሰራቻቸው አንድ አንድ ስህተቶች ምክንያት በስልጣን በነበረችበት ዘመን የነበረው እድገትና ሰላም እርሷ ስታልፍ አብሮ አለፏል። እንግዴህ አገሪቱ ወደ ዘመነ መሳፍንት የተሻገረችው ልክ እርሷ እንዳለፈች ነበር።
==
Quick Facts እቴጌ ምንትዋብ, ባለቤት ...
እቴጌ ምንትዋብ | |
---|---|
ባለቤት | ዐፄ በካፋ ምልምል ኢያሱ |
ልጆች | ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወይዘሮ አስቴር ወለተ እስራኤል ወይዘሮ አልጣሽ |
ሙሉ ስም | ንግሥት ብርሃን ሞገስ (የዙፋን ስም) ወለተ ጊዮርጊስ (የክርስትና ስም) |
ሥርወ-መንግሥት | ሰሎሞን |
አባት | ደጅአዝማች መንበር |
እናት | ልዕልት እንኳይ |
የተወለዱት | ፲፯፻፮ ዓ.ም. እ.ኤ.አ |
የሞቱት | ግንቦት ፳፯ ቀን ፲፯፻፸፫ ዓ.ም. እ.ኤ.አ |
የተቀበሩት | ደብረ ፀሐይ ማርያም |
ሀይማኖት | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና |
Close
==