አይቲዮፒያ (የግሪክ ቃል)
From Wikipedia, the free encyclopedia
አይቲዮፒያ (ግሪክ፦ Αιθιοπία፣ ሮማይስጥ፦ Aethiopia) የሚለው ቃል መጀመርያ በጥንታዊ ምንጮች የመልክዓ ምድር ስያሜ ሆኖ ሲታይ፣ የላየኛ አባይ ወንዝ አውራጃ እንዲሁም ከሳህራ በረሃ በስተደቡብ ላለው አገር በሙሉ ያመለከት ነበር። ይህ ስም በግሪክ በሆሜር ጽሁፎች በኢልያዳና ኦዲሲ (ምናልባት 850 ዓክልበ.) ብዙ ጊዜ ይጠቀሳል። በተለይ ከግሪክ ታሪክ ምሁር ሄሮዶቱስ (440 ዓክልበ. ግድም) ጀምሮ «አይቲዮፒያ» ሲጻፍ ትርጉሙ ከግብጽ ወደ ደቡብ ለተገኘው የአፍሪካ ክፍል ሁሉ እንደ ሆነ ግልጽ ነው።