አሪስጣጣሊስ
From Wikipedia, the free encyclopedia
አሪስጣጣሊስ በግሪኩ Ἀριστοτέλης ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ384 ዓ.ዓ. እስከ ታህሳስ7፣ 322ዓ.ዓ. የኖረ የጥንቱ ግሪክ ፈላስፋ ነበር። በምዕራቡ አለም ስልጣኔ ከፍተኛ ግምት ያለው ፈላስፋ ነበር። ምንም እንኳ አሪስጣጣሊስ ብዙ መጻሕፍትን የጻፈ ቢሆንም ዘመናትን አልፈው ተርፈው የሚገኙት መጻሕፍት ጥቂት ናቸው። የፕላቶ ተማሪ የሆነው አሪስጣጣሊስ በተራው የንጉሱ ታላቁ እስክንድር አስተማሪ የነበርና ንጉሱ በእድሜ ጎልምሶ የዚያን ዘመን አለም በሚገዛ ወቅት በስሩ ከሚያስገብራቸው እንግዳ አገሮች እጽዋትንና እንሣትን ለፈላስፍው መምህሩ ይልከለት ነበር።