ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲናግዴ ከኦሮሞ ገበሬ አባታቸው ከአቶ ዲነግዴ ቦተራ እና የሰባት ቤት ጉራጌ ቦዞ ሰንጌ ከሆኑት እናታቸው ከእመት ኢጁ አመዲና በሺ ስምንት መቶ አርባ ሶስት እና አርባ አራት አካባቢ ፣ በአመያና ወሊሶ አካባቢ ተወለዱ፡፡ በአድዋ ዘመቻ ጊዜ በአሽከር ብዛትና በደግነት ሥራ በጣም የተመሰገኑት ሀብተ ጊዮርጊስ በ1889 ዓ.ም. ፊታውራሪ ተብለው የጦር አበጋዝነቱን ተሹመዋል፡፡