ጅማ ዩኒቨርስቲ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ጅማ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንዱ ነው። ይህ ተቋም የሚገኘው በኦሮሚያ ክልል፣ ጅማ ዞን (ጅማ) ውስጥ ነው። ተማሪዎችን በተለያዩ ዘርፎች በዲግሪ እና በተለያዩ ደረጃዎች ያሠለጥናል። በቀድሞው ስሙ ጅማ የግብርና ኮሌጅ እና የጅማ የጤና ሳይንስ ተቋም በጋራ የነበረ ሲሆን ከታኅሣሥ 1992 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ዩኒቨርስቲ ሊያድግ ችሏል። ዋናው ካምፓስ የሚገኘው ከቀድሞው የጅማ ንጉስ አባ ጅፋር ቤተ መንግስት ቀጥሎ ነው።