![cover image](https://wikiwandv2-19431.kxcdn.com/_next/image?url=https://upload.wikimedia.org/wikipedia/am/thumb/9/9b/%25E1%258B%25AD%25E1%2588%259D%25E1%2588%25AD%25E1%2588%2583%25E1%258A%2590%25E1%258A%25AD%25E1%2588%25AD%25E1%2588%25B5%25E1%2589%25B6%25E1%2588%25B5_%25E1%258B%258B%25E1%2588%25BB.jpg/640px-%25E1%258B%25AD%25E1%2588%259D%25E1%2588%25AD%25E1%2588%2583%25E1%258A%2590%25E1%258A%25AD%25E1%2588%25AD%25E1%2588%25B5%25E1%2589%25B6%25E1%2588%25B5_%25E1%258B%258B%25E1%2588%25BB.jpg&w=640&q=50)
ይምርሃነ ክርስቶስ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ይምርሃነ ክርስቶስ በ ዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ አነሳሽነት በ12ኛው ክፍለ ዘመን በአቡነ ዮሴፍ ተራራ ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ የተሰራ ቤተክርስቲያንና በዚያው ዋሻ ውስጥ ከቤተርክስቲያኑ ፊትለፊት ያለ ቤተ መንግስት ህንጻ በአንድነት የሚጠሩበት ስም ነው። ዋሻው ከላሊበላ የ6 ሰዓት የእግር ጉዞ ርቀት ላይ ይሚገኝ ሲሆን 45ሜትር ርዝመት በ6 ሜትር ቁመትና 50ሜትር ጉድጉደት አለው። በዋሻው ውስጥና ውጭ ለጸበል የሚያገለግሉ ምንጮች ይፈልቁበታል። ዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ ከሮሃ ሆኖ አገሩን ያስተዳድር እንጂ ይሄው ቤተክርስቲያንና ቤተመንግስት ሲታነጽ መኖሪያውን ወድዚህ ዋሻ እንዳዛወረ በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ የህይወት ታሪኩ ይገልጻል። በ16ኛው ክፍልዘመን መጀመሪያ ኢትዮጵያን ጎብኝቷት የነበረው አልቫሬዝ እንዲሁ በዚህ ቤተክርስቲያን ለ2 ቀን ቆይታ በማድረግ ገድለ ይምርሃነ ክርስቶስ የተሰኘ መጽሐፍ እንዳነበበና እንደመረመረ ያትታል[1]።
Quick Facts ከአለት የተፈለፈለ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን, ይምርሃነ ክርስቶስ ...
| ||||
---|---|---|---|---|
ይምርሃነ ክርስቶስ | ||||
[[ስዕል: ![]() | ||||
ከግራ ወደቀኝ፡ መቃብሮች፣ ቤተክርስቲያን፣ ቤተመንግስትና አጽማት ማረፊያ | ||||
አገር | ኢትዮጵያ | |||
ሌላ ስም | {{{ሌላ ስም}}} | |||
ዓይነት | ዋሻ ውስጥ የሚገኝ | |||
አካባቢ** | አቡነ ዮሴፍ ተራራ | |||
የቅርስነት ታሪክ | ||||
ቅርሱ የተሰራበት ዘመን | 12ኛው ክፍለ ዘመን | |||
አደጋ | ቤተመንግስት ጣራና ወለል | |||
* የአለበት ቦታ ** የዩ.ኔ.ስ.ኮ. ክልል ክፍፍል |
Close