ታኅሣሥ ፫
- ይቺ ዕለት በኢትዮጵያ ታሪክ ሁነኛ ስፍራ አላት። ታላቁ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክና የጦሩ ፊታውራሪ፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ ያረፉበት ዕለት ናት። ዕለቱ ተመሳሳይ ይሁን እንጂ ሁለቱ ያረፉት በተለያዩ ዓመታት ነው። ‹‹አባ ዳኘው›› የተባሉት፣ ዳግማዊ ምኒልክ ፳ኛው ምዕት ዓመት በባተ በስድስተኛው ዓመት ላይ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. ሲያርፉ ‹‹አባ መላ›› የተሰኙት ፊታወራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ደግሞ በ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. አርፈዋል። ዓመታቱ ይለያዩ እንጂ ሁለቱም ያረፉት ዓርብ ታኅሣሥ ፫ ቀን ነበር።
- ፲፰፻፲ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የዘመነ መሣፍንት ሲጀመር ከዙፋናቸው ወርደው አክሱም በስደት ላይ የነበሩት እና “ተፍጻሜተ ነገሥት” የሚባል ቅጽል ስም የተሰጣቸው ቀዳማዊ ዓፄ ተክለ ጊዮርጊስ አረፉ።
- ፲፱፻፮ ዓ/ም - መጀመሪያ የሸዋ ንጉሥ በኋላም የዘመናዪቱ ኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት፤ በአድዋ ጦርነት የኢጣሊያን ሠራዊቶች ድል የመቱት ታላቁ መሪ፤ “ዕምዬ ምኒልክ” ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ባደረባቸው ህመም በዛሬው ዕለት አረፉ።
- ፲፱፻፰ ዓ/ም - የቻይና ሪፑብሊክ ፕሬዚደንት አገሪቱን ወደንጉዛት ሥርዐት መመለሳቸውንና እራሳቸውንም ንጉሠ ነገሥት ማድረጋቸውን አወጁ።