From Wikipedia, the free encyclopedia
የዓፄ ላሊበላ ተከታይ እና የዛግዌ ሥርወ መንግስት የመጨረሻ ንጉሥ የሆኑት ዓፄ ነዓኩቶ ለአብ አሁን በርሳቸው ስም በሚጠራ መንደር አቅራቢያ በሚገኝ ዋሻ ስር ያሰሩት ቤተከርስቲያን ነው። አቀማመጡም ከላሊበላ በስተደቡብ ምስራቅ 6 ኪሎ ሜትር ርቆ ነው። ቤተርክስቲያኑ በመጠን አነስተኛ ሲሆን ከተሰራበት ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ከበላዩ ዋሻ ሳይደርቅ በሚፈስ የምንጭ ውሃው ይታወቃል። እንዲሁም ይህን ውሃ ለማጠራቀም የሚረዱ፣ በጊዜ ሂደት የጎደጎዱ ደንጋዮች ከቤተርክስቲያኑ ጥንታዊ የመጻሕፍት፣ መስቀሎችና ሙዳዮች ቅርስ ተርታ ይመደባሉ። በነዓኩቶ ለአብ ዋሻ ውስጥ ሌላው ጎላ ብሎ የሚታየው ንግሥት ዘውዲቱ በ20ኛው ክፍለ ዘመን ያሰሩት ከቀይ ጡብ የተሰራ አነስተኛ ህንጻ ነው።
| ||||
---|---|---|---|---|
ነዓኩቶ ለአብ | ||||
የነዓኩቶ ለዓብ ቤተርክስቲያን የውጭ ገጽታ። | ||||
አገር | ኢትዮጵያ | |||
ዓይነት | የዋሻ ውስጥ ቤተርክስቲያን | |||
አካባቢ** | ላስታ | |||
የቅርስነት ታሪክ | ||||
ቅርሱ የተሰራበት ዘመን | 13ኛው ክፍለዘመን | |||
አደጋ | አይታዎቅም | |||
* የአለበት ቦታ ** የዩ.ኔ.ስ.ኮ. ክልል ክፍፍል |
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.
Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.