ቀቿ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ቀቿ (Qhichwa Simi / Runa Shimi / Runa Simi) በደቡብ አሜሪካ በ10 ሚሊዮን ሰዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በጥንታዊ ኢንካ መንግሥት መደበኛ ቋንቋ ነበረ። ዛሬም በቦሊቪያ ፔሩና አንዳንድ አውራጃ በኤክዋዶር መደበኛ ሁኔታ አለው። አይማራ የሚባለው ሌላ ደቡብ-አሜሪካዊ ቋንቋ ዘመድ ነው።
እስፓንያውያን ከወረሩ አስቀድሞ በሰፊ ይሰማ ሲሆን በዚያን ጊዜ ምንም ጽሕፈት አልነበረውም። ይሁንና መቆጣጠር ሲባጎዎች በማሰር ዘዴ ነበር የተፈጸመ። ዛሬ የሚጻፈው በላቲን ፊደል ነው።