ማይክል አንጄሎ ቡናሮቲ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ማይክል አንጄሎ ዲ ሎዶቪኮ ቡናሮቲ ሲሞኒ (6 ማርች 1475 - 18 ፌብሩዋሪ 1564) በተለምዶ ማይክል አንጄሎ እየተባለ ይጠራ የነበረው የእንደገና መወለድ ተብሎ በሚጠራው ዘመን ይኖር የነበረ ኢጣሊያዊ ሰዓሊ ፤ ቀራጭ፤ ህንጻ ሰሪ፤ ገጣሚ፤ እና መሀንዲስ ነበር። ምንም እንኳን ቅንድብን ወደ ላይ ከማስነሳቱ ባሻገር ይጠቀምባቸው የነበረው ስነ ስርአቶች እጅግ በጣም ከፍተኛ ደረጃ በመሆናቸው የእንደገና መወለድ ሰው የሚል ቅጽል ስም አሰጥቶት ነበር። እሱን በመሳሰሉ ታላላቅ ሰዓሊዎች ለምሳሌ ሊዮናርዶ ዳቪንቺ። ማይክል አንጄሎ በረጅም የእድሜ ዘመኑ በሰራቸው በማናቸውም የስራ ውጤቶቹ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነበሩ። ታሪካቸው በደንብ ከተመዘገበላቸው የ16ኛው ክፍለ ዘመን ሰአሊዎችም አንዱ አድርጎታል። እጅግ በጣም ከሚወደዱት ሁለት ስራዎቹ መሀከል ፒየታ = ሐዘን እና ዳዊት የሚባሉትን ሰርቶ የጨረሰው እድሜው ሠላሳ ከመሆኑ በፊት ነበር። ምንም እንኳን ለስዕል የነበረው አመለካከት በጣም ዝቅተኛ ቢሆንም ማይክል አንጄሎ ሁለት ድንቅ የተባሉ ስእሎችን በጄሶ ላይ በመስራት ለምዕራቡ አለም አበርክቷል። ዘፍጥረትን ሲስቲኒ በሚባለው ቤተ ክርስቲያን ጣራ ላይ እና የፍርድ ቀን የተባለውን ደግሞ በሲስቲኒ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከመንበሩ በስተጀርባ በኩል በሮማ ከተማ ውስጥ ይገኛሉ። ማይክል አንጄሎን ልዩ ከሚያደርገው አንዱ ነገር የመጀመሪያው የምእራብ አለም ሰዓሊ በህይወት ዘመኑ እያለ የህይወት ታሪኩ የተጻፈለትም በመሆኑ ነው። ሁለት የተለያዩ ጸሃፊዎች በህይወት እያለ ታሪኩን ጽፈውታል። አንደኛው ጂዮርጂዮ ቫሳሪ ሲሆን እርሱም ማይክል አንጄሎ እንደገና መወለድ ካፈራቻቸው የኪነ ጥበብ ሰዎች አናት ነው ብሎ ከፍተኛውን ስፍራ ይሰጠዋል። እስከ አሁን ድረስም ይህ አባባል እንደቀጠለ ይገኛል። በህይወት ዘመኑም እያለ የተቀደስው ወይም የተባረከው የሚል ቅጽል ስም አሰጥቶት ነበር[13]።