ሄክታር
From Wikipedia, the free encyclopedia
ሄክታር የአለም አቀፍ ክልል መለኪያ ሲሆን፣ ትርጉሙ በየጎኑ አንድ መቶ ሜትር ያለው ካሬ (አራት ማዕዘን ያለው) ክልል ስፋት ማለት ነው።
ቃሉ (በፈረንሳይኛ በኩል) የደረሰው ከግሪክኛ ἑκατόν /ሄካቶን/ «መቶ»፣ እና ሮማይስጥ area /አሬያ/ «ክልል» ነበር።
ሄክታር ስለዚህ አሥር ሺህ ካሬ ሜትር አለበት። ሄክታር በተለይ ለመሬት (ርስት ወይም እርሻ) ክልል ለመለካት ይጠቀማል።
- 1 ሄክታር = 10,000 ካሬ ሜትር
- 1 ሄክታር = የራግቢ ሜዳ የሚያህል ክልል፣ 100x100 m
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |